Theme images by kelvinjay. Powered by Blogger.

Slider

ESAT

Ethiopian News

Movies

Drama

Sport

Opinion

History

የጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት ስልጣን ለቀቁ



የጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት ስልጣን ለቀቁ

(ኢሳት ዲሲ–ጥቅምት 16/2011) የጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት ስልጣናቸውን ለቀቁ። አዲስ ፕሬዝዳንትም ተሰይሟል።

በአዲስ አበባ ለአንድ ሳምንት ግምገማ ሲያደርግ የቆየው የጋምቤላ ክልል ገዢ ፓርቲ በገዛ ፈቃዳቸው የለቀቁትን ሊቀመንበሩንና ምክትላቸውን በሌሎች መተካቱን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።

የጋምቤላ ህዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀመንበርና የጋምቤላ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ጋትሉዋክ ቱትና ምክትላቸው አቶ ሰናይ አኩዎር ይቅርታ ጠይቀው በለቀቁበት የአዲስ አበባው ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መገኘታቸውን ለማወቅ ተችሏል።

በጋምቤላ የጋትሉዋክ ቱት አመራር ከስልጣን እንዲወርድ የተቃውሞ ሰልፍ ሲደረግ ቆይቷል። በዚህ ተቃውሞ በተወሰደ የሃይል ርምጃም በትንሹ አስር ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል። ለወራት የዘለቀው የህዝብ ጩሀት በመጨረሻም ሰሚ አገኘ።

የጋምቤላ ክልል ነዋሪ አመራሩ እንዲነሳለት ህይወቱን የገበረለትን ተቃውሞ ሲያደርግ ነበር የቆየው። ባለፉት ሶስት ወራት በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የክልሉ ተወላጆች ለፌደራሉ መንግስት ጥያቄ ሲያቀርቡ እንደነበር ይታወሳል።

በአመራር ላይ ያለው የጋትሉዋክ አስተዳደር በኢትዮጵያ የመጠውን የለውጥ ሂደት የሚያደናቅፍ ከመሆኑ ባሻገር የህወሀት የጭቆና አገዛዝን ማስቀጠል የመረጠ በመሆኑ በአስቸኳይ ይነሳ የሚለው ጥያቄ ተነስቷል።

ተቃውሞው በተለይ የክልሉ ፕሬዝዳንት ላይ ያነጣጠረ ነበር።

ለዚህም ሁለት ምክንያቶች ይነሳሉ። አንደኛው የክልሉ ፕሬዝዳንት ጋትሉዋክ ቱት በትውልድ ደቡብ ሱዳናዊ በመሆናቸው በስደት ወደኢትዮጵያ ለገቡትና በቁጥር በጋምቤላ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን ለሚበልጡ ደቡብ ሱዳናውያን ያደላሉ የሚል ነው።

ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ከህወሀት አገዛዝ ጋር እጅና ጓንት ሆነው የክልሉን ህዝብ ለጭቆናና ብዝበዛ እየዳረጉት እንደሆነ ይጠቀሳል።

የህወሃት ዘመን አፈናና በደል ጋምቤላ ተጠናክሮ መቀጠሉን ህዝቡ በምሬት ይገልጻል።

በቅርቡ ለውጡን ለመታዘብ ሀገር ቤት የገቡትን በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆኑት ዶክተር ማኛንግን ጨምሮ ከ10 በላይ አክቲቪስቶችን የግትሉዋክ ቱት አስተዳደር ማሰሩ ተቃውሞውን አጠናክሮታል።

የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ፕሬዝዳንት አቶ ኦባንግ ሜቶ ወደ ጋምቤላ ባመሩ ጊዜ የጋቱዋክ ቱት አመራር የፈጠረውን ችግር መነሻ በማድረግ በአዲስ አበባ መግለጫ የሰጡት አቶ ኦባንግ የፌደራሉ መንግስት በጋምቤላ አስተዳደር ላይ እርምጃ እንዲወስድ መጠየቃቸውም የሚታወስ ነው።

ለወራት የህዝብ ብሶትና እሮሮ ከተሰማ በኋላ ትላንት ምላሽ መገኘቱን ነው የደረሰን መረጃ የሚያመለክተው።

አዲስ አበባ የገቡትና ግምገማቸውን ከጀመሩ አንድ ሳምንት የሆናቸው የጋምቤላ ህዝቦች አንድነት ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ጋህአዴን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ከአንድ ውሳኔ ላይ መድረሳቸውን አሳውቀዋል።

ህዝብ ለውጥ እንደሚፈልግ፣ አመራሩ እንቅፋት ሆኖ እንደቆየ አባላቱ ጠንከር ያለ ግምገማ ማድረጋቸውን ተከትሎ የህዝብ ተቃውሞ የቀረበባቸው አቶ ጋትሉዋክ ቱትና ምክትላቸው አቶ ሰናይ አኩዎር በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸውን መልቀቃቸው ተስምቷል።

ፓርቲው አቶ ኦሙድ ኡጁሉን የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አኙአያ ጃከን ደግሞ ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡም ታውቋል፡፡ አቶ ኦሙድ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ክልሉን እንደሚመሩ ነው የተገለጸው።

በግምገማው ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ መገኘታቸው ታውቋል።

የክልሉ ህዝብ ልማት የተጠማ በመሆኑ አዲሱ አመራር ጊዜውን በግል አጀንዳዎችና ሽኩቻ ከማጥፋ ይልቅ ራሱን ከጎሰኝነትና ከጥላቻ በማጽዳት የክልሉን አመራር በማጠናከር የህዝቡን ችግር ሊፈታ እንደሚገባ ማስገንዘባቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍጹም አረጋ ገልጸዋል።

ከኃላፊነት የተነሱት አመራሮችም በድርጊታቸው ተጸጽተው ይቅርታ መጠየቃቸው እና ህዝቡን ለመካስ በተመደቡበት የስራ መስክ ለመሰማራት መወሰናቸውም ተመክልቷል።

ኢሳት ያነጋገራቸው የጋምቤላ አክቲቪስቶች ግን የጋትሉዋክ አመራር አባላት ለፈጸሙት የግድያና የዘረፋ ወንጀል በህግ ሊጠይቁ ይገባል ባይ ናቸው።


የአቶ አለነ ማህፀንቱ የፍርድ ቤት ውሎ ከእዮዔል ፍሰሃ

የአቶ አለነ ማህፀንቱ የፍርድ ቤት ውሎ ከእዮዔል ፍሰሃ

  • የፓርቲው የቀድሞ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለን ጨምሮ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል
  • ተከሳሹም ለፍርድ ቤቱ የተከሳሽነት ቃላቸውን ሰጥተዋል
‹‹ስብሰባን በማወክ ወንጀል›› የተከሰሱት የቀድሞ አንድነት ፓርቲ ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊና ብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ አለነ ማህፀንቱ፣ በፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 5ኛ ወንጀል ችሎት በመቅረብ መከላከያ ምስክሮቻቸውን አሰሙ፡፡

ችሎቱ ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ላይ የአቶ አለነ ማህፀንቱን መከላከያ ምስክሮች ለማዳመጥ የተሰየመ ሲሆን፤ በችሎቱ የተሰየሙት ዳኛ፣ ተከሳሹ የተከሳሽነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ጠይቀዋል፡፡ አቶ አለነ ማህፀንቱም የተከሳሽነት ቃላቸውን በሚከተለው መልኩ ለፍርድ ቤቱ አቅርበዋል፡፡

‹‹ስሜ አለነ ማህፀንቱ ይባላል፡፡ ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነኝ፡፡ በትምህርቴ የማስተርስ ዲግሪ ባለቤት ነኝ፡፡ በሙያዬ የተለያዩ ቦታዎች ሰርቼያለሁ፤ በተለያዩ ኮሌጆች ላይ ዲን ሆኜ ሰርቼያለሁ፡፡ በትምህርት ቤቶችም በርዕሰ መምህርነት አገልግያለሁ፡፡ በሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የፖሊሲና ፕሮግራም ኃላፊ ሆኜ ሰርቼያለሁ፡፡ ሀገሬን ወክዬ በተለያዩ ሀገራት በመጓዝ ተከራክሬያለሁ፡፡ 


የሀገሬን ጥቅምም አስከብሬያለሁ፡፡ በፖለቲካ ዘርፍ የ11 ዓመት ልምድ አለኝ፡፡ ለተወካዮች ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ ሆኖ ከመቅረብ አንስቶ፤ በአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ብሔራዊ የስራ አስፈፃሚ አባል፣ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል እንዲሁም የማህበራዊ ጉዳዮች ኃላፊ ሆኜ እስከተያዝኩበት ቀን ድረስ አገልግያለሁ፡፡ የታሰርኩበትና የተያዝኩበት ምክንያትም በፖለቲካ አመለካከቴ ነው፡፡  

የተቃውሞ ጎራ አባል በመሆኔና እኔም ስታገል የነበርኩት በሀገሬ ላይ ዲሞክራሲን ለማስፈን፤ የፍትሕ ተቋማት ገለልተኛና ነፃ ሆነው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ፤ ዜጎች ያለምንም ምክንያት የማይታሰሩባት ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ፣ ትክክለኛ ፍትህ በሀገሪቱ እንዲሰፍን፣ ትክክለኛ ዲሞክራሲ እውን እንዲሆን ነው፡፡ 

እንደ ተማሩ ወጣቶች ሁሉ ለሀገሬ ሰርቼያለሁ፡፡ በዚህ ስብእናዬ፣ በአካዳሚክ ባክግራውንዴ፣ ባለኝ ማህበራዊ ኃላፊነት አሁን የተከሰስኩበትን ክስ ማለትም አቃቤ ሕግ ያቀረበውን ‹‹አይኤስን ምክንያት በማድረግ መንግስትን በሀይል ለመናድ….›› ወዘት የሚሉ ነገሮች፤ የቀረቡብኝ ባለኝ የፖለቲካ አመለካከት ነው፡፡  

በክሱ ላይ የተዘረዘሩት ነገሮች ሁሉ ባለኝ የፖለቲካም ሆነ የማህበራዊ ኃላፊነቴ ልፈፅማቸው የማልችላቸው መሆኔን አረጋግጬ መናገር እፈልጋለሁ፡፡ በዚህም ምክንያት ሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም ከቤቴ በማይታወቁ ሰዎች ታፍኜ ተወስጄያለሁ፤ ከምኖርበት አካባቢ በአራት ደህንነቶች ታፍኜ ተወስጄ ክስ ተመስርቶብኝ፤ በሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በተጠራው ሰልፍ ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግርም ሆነ የሌሎችን ንግግር ለመግታት፣ ‹‹ጉባኤ አውከሃል›› በሚል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 490/3 በመናገሻ ፍርድ ቤት ቀርቤ፤ የአቃቤ ሕግ ምስክር በፖለቲካ ሴራና በተንኮል የተደራጀ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ስላረጋገጠ በነፃ አሰናብቶኛል፡፡

ይህንንም የተከበረው ፍርድ ቤት አምጥቶ ያረጋገጠ ይመስለኛል፡፡ የመናገሻ ፍርድ ቤት በነፃ ካሰናበተኝ በኋላ፤ የኢህአዴግ መንግስት እኔን ማሰር አላማው አድርጎ ስለተንቀሳቀሰ ብቻ በሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም ከሶኝ የነበረውን ክስ ሰርዞ፤ ‹‹በሚያዚያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ለቅሶ ቦታ ላይ ተገኝተህ አመፅ ለማነሳሳት ሞክረሃል›› በማለት ክስ አቅርቦብኛል፡፡ ይህ ክስ እኔንም ሆነ ፍርድ ቤቱን የማይመጥን ክስ ነው፡፡ 

‹‹ወጣቶችን አደራጅትህ በሪቼ አድርገህ፣ ወደ መስቀል አደባባይ ወስደሃል›› የሚል ክስ ነው የቀረበብኝ፡፡ የሀሰት ምስክሮች ማለትም፡- የቀበሌ አመራሮች፣ የፎረም አባሎች፣ ሰብስቦ በማምጣት በሀሰት ተመስክሮብኝ እንዲህ አይነት ክስ ሊመሰረትብኝ ተችሏል፡፡ በዚህች ሀገር ላይ የመኖር ዋስትናዬ አልተከበረልኝም፤ እየተከበረልኝም አይደለም፡፡

ስለዚህም የተከበረው ፍርድ ቤት ጭብጥ ማስያዝ የምፈልገው በወቅቱ እኔ ከ2፡30 እስከ 3፡00 ባለው ግምታዊ ሰአት ከጓደኞቼ ጋር ማለትም ከአቶ ግርማ ሰይፉ ቢሮ መገኘቴን ነው፡፡ ‹‹ሙሾ እያወረደ ሲያሳምፅ ነበር›› የሚለው የፈጠራ ክስ በጭራሽ የማይገናኝ ነው፡፡ ከእነዚህው ጓደኞቼ ጋር እስከ ምሳ ሰዓት አብሬ ነበርኩ፡፡›› በማለት የተከሳሽነት ቃላቸውን ለፍርድ ቤቱ ሰጥተዋል፡፡

በፍርድ ቤቱ የተሰየሙት ዳኛ ለአቶ አለነ ማህፀንቱ የተወሰኑ የማጣሪያ ጥያቄዎችን ካቀረቡ በኋላ የተከሳሹን መከላከያ ምስክሮች አድምጠዋል፡፡ 1ኛ ምስክር አቶ ግርማ ሰይፉ ከተከሳሹ ጋር በነበራቸው ቀጠሮ መሰረት ሚያዚያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 አካባቢ ቄራ በሚገኘው ቢሯቸው መገናኘታቸውንና ዮናስ ጨርጨር፣ ተብሎ በሚጠራው ሥጋ ቤት አብረው ምሳ መብላታቸውንና እስከ 9፡00 ድረስ አንድ ላይ እንደነበሩ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ 

በመጨረሻም ስቴዲየም አካባቢ መለያየታቸውን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ ከአቃቤ ሕግ በኩል ለተነሱ መስቀለኛ ጥያቄዎችም ምላሻቸውን ሰጥተዋል፡፡ ከፍርድ ቤቱ በኩልም ለተነሳላቸው የማጣሪያ ጥያቄ ምላሻቸውን አስከትለዋል፡፡ በተመሳሳይ 2ኛው ምስክር አቶ ተክሌ በቀለና 3ኛው ምስክር አቶ ስዩም መንገሻ ተመሳሳይ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡  

አቃቤ ሕግ ለአቶ ተክሌም ሆነ ለአቶ ስዩም መንገሻ መስቀለኛ ጥያቄን አንስቷል፡፡ አቶ ተክሌ በቀለም ሆነ አቶ ስዩም መንገሻ ከፍርድ ቤቱ የማጣሪያ ጥያቄ አልቀረበላቸውም፡፡

የፓርቲው የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ግርማ ሰይፉ፣ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አቶ ተክሌ በቀለና የፓርቲ ዋና ፀሐፊ የነበሩት አቶ ስዩም መንገሻ፣ መከላከያ ምስክር በመሆን የምስክርነት ቃላቸውን ለፍርድ ቤቱ ሰጥተዋል፡፡ አቶ አለነ በመከላከያ ምስክርነት አራት ሰዎችን ቢያስመዘግቡም፤ አራተኛ ምስክራቸው የነበሩት የፓርቲው የቀድሞ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃም፣ የምስክርነት ቃላቸውን ሳይሰጡ ቀርተዋል፡፡  

የተከሳሹ ጠበቃ አቶ ሽብሩ በለጠ፣ ‹‹ሶስቱ የመከላከያ ምስክሮች ከሰጡት የምስክርነት ቃል ጋር ተመሳሳይ የሆነ ነገር ሊናገሩ ስለማይችሉ፤ ሶስቱ ምስክሮች በቂ ናቸው፡፡›› በማለት ጠበቃው አስተያየታቸውን መስጠታቸውን ተከትሎ የምስክርነት ቃላቸውን ሳይሰጡ ቀርተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠ ሲሆን፤ ብይን ለማስተላለፍ ተለዋጭ ቀጠሮ ለጥቅምት 24 ቀን 2008 ዓ.ም ሰጥቷል፡፡

በወጣቶች መካከል እየተፈጠረ ያለውን ግጭትና ህገ ወጥ ተግባር ከዚህ በኋላ እንደማይታገስ የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ



ፌደራል ፖሊስ

(ኤፍ.ቢ.ሲ) ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ የድርጅት አመራሮችን ለመቀበል በሚደረግ ቅድመ ዝግጅት ላይ በወጣቶች መካከል እየተፈጠረ ያለውን ግጭትና ህገወጥ ተግባር ከዚህ በኋላ እንደማይታገስ የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል ከአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር የስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ኢብሳ ነገዎ ጋር በመሆን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው ላይም ኮሚሽነር ዘይኑ ጀማል በትናንትናው እለት እና ዛሬ ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ የድርጅት አመራሮችን ለመቀበል በሚደረግ ቅድመ ዝግጅት ላይ በወጣቶች መካከል ግጭት መፈጠሩን አስታውቀዋል።

በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራውን የኦነግ ቡድን ለመቀበል እየተደረገ ባለ ቅድመ ዝግጅት ወቅት ወጣቶች የድርጅቱን አርማ ለመስቀል ዝግጅት እያደረጉ ነበር፤ ይህንን የከለከላቸው አካል የለም ያሉት ኮሚሽነር ዘይኑ፥ ሆኖም ግን አስፋልትን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትን እንዳያቀልሙ ተከልክው የነበረ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚሁ ጉዳይ ላይም የሃሳብ ልውውጥ ከተደረገ በኋላ ወጣቶቹ የቀረበውን ሀሳብ ተቀብለው የነበረ መሆኑን ተናግረዋል።


ሆኖም ግን ማንም ያልፈቀደላቸው አካላት የእነሱን አርማ አውርደው የሌላ ለመስቀል ሲሉ ግጭት ተፈጥሯል ሲሉም ገልፀዋል።

ግጭቱ ለማንም ጠቃሚ አይደለም ያሉት ኮሚሽነር ዘይኑ፥ ችግሩን በውይይት መፍታት ሲቻል ወደ አላስፈላጊ ግጭት መግባት ተገቢ አይደለም ሲሉም ተናግረዋል።

ፖሊስ የህግ የበላይነትን የማስከበር ሀላፊነት ስላለበት ከዚህ በኋላ እንዲህ አይነት ግጭቶችን በትእግስት እንደማያልፍም ኮሚሽነር ዘይኑ አሳስበዋል።

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፥ የዴሞክራሲ ስርዓትን እንገንባ ብለን ስንነሳና ስርዓቱን ለመገንባት የሚያስፈልጉ ባህሪያትን ተቀብለን ካልተነሳን ግን ስርዓቱን መገንባት እንችልም ብለዋል።

የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ውስጥ ልዩነቶችን መቀበል የግድ ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፥ ልዩነቶቹ ደግሞ ሀሳቦችን፣ አርማዎችን እና ባንዲራዎችን ሊያጠቃልል ይችላል ብለዋል።

ትናንትና እና ዛሬ በአዲስ አበባ የተስተዋሉ ችግሮች ደግሞ ከዚህ ጋር የሚፃረሩ ናቸው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፥ ማንኛውም አካል ስሜቴን ይገልፅልኛል ያለውን አርማ የመያዝ እና የማውለብለብ መብት አለው ሲሉም ተናግረዋል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ኢብሳ ነገዎ በበኩላቸው፥ ሰሞኑን በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ የተስተዋለው ችግር ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አንስተዋል።

ወጣቱም ከዚህ አይነት እንቅስቃሴዎች ሊቆጠብ እንደሚገባም አቶ ኢብሳ ጥሪ አስተላልፈዋል።

አሁን ላይ እየታየ ያለው ግጭት እና ያልተገባ ፉክክር ድርጅታቸውን የማይወክል መሆኑንም ነው አቶ ኢንብሳ የተናገሩት።

የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ለአዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ (ኤፍ.ቢ.ሲ)

 የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ተቀማጭነታቸውን በኢትዮጵያ ያደረጉ የበርካታ ሀገራት አምባሳደሮች ለ2011 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ የደስታ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የአሜሪካው አምባሳደር ማይከል ራይነር፥ ለሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች መልካም አዲስ ዓመት አንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገለፅዋል።

አምባሳደሩ አክለውም አዲሱ የ2011 ዓመት ለኢትዮጵያውያን ከዚህ ቀደም ከነበሩ አዲስ ዓመቶች በበለጠ ተስፋን ይዞ የመጣ ነው ያሉ ሲሆን፥ ይህ ተስፋ እውን እንዲሆንም ሁላችንም የበኩላችንን ልንወጣ ብለዋል።

አምባሳደሩ አክለውም፥ በአዲሱ ዓመት የህዝቡን አንድነት ለመከፋፈል እና ብጥብጥ ለማስነሳት የሚነዙ ሀሳቦችን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊከላከለው እና አንድነቱን በሚያጠባክሩ ጉዳዮች ላይ ሊያተኩር ይገባል ሲሉም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ሁሉም የአሜሪካ ኤምባሲ ሰራተኞች በአዲሱ የ2011 ዓመት ለኢትዮጵያ እድገት የበኩላቸውን ለመወጣት ከምንጊዜውም በበለጠ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በተመሳሳይ የቱርክ አምባሳደር ፋቲህ ኡሉሶይ፥ መጪው አዲስ ዓመት ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት የስኬት ዘመን እንዲሆን፣ የበለጠ ጠንካራ፣ የተረጋጋች እና የበለጸገች ኢትዮጵያን የምናይበት ዘመን እንዲሆን እንመኛለን ብለዋል።

የህንድ አምባሳደር አኑራግ ስሪቫስታቫ በበኩላቸው፥ በኢትዮጵያ የተጀመረው የይቅርታና የእርቅ ሂደት እንዲሁም በሀገሪቱ ብሎም በቀጠናው ተስፋ የፈነጠቁት ጥልቅ ማሻሻያዎች ከግብ የሚደርሱበት ዓመት እንዲሆን ተመኝተዋል።

የስዊድን አምባሳደር ቶርብጆርን ፔተርሰን በኢትዮጵያ የሚታየው የዴሞክራሲ ተስፋ እንዲሁም ፈርጀ ብዙ ማሻሻያዎች ተጠናክረው የሚቀጥሉበት ዓመት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የደቡብ ሱዳን አምባሳደር ጃመስ ሞርጋን፥ አዲሱ ዓመት ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ በሀገራቸው እንዲሁም በቀጠናው ያመጡት የሰላምና ብልፅግና ጮራ ይበልጥ የሚያበራበት ዘመን እንዲሆን ተመኝተዋል።

የዴንማርክ፣ ፊንላንድ ፣ ኮሪያ እና አውስትራሊያ አምባሳዳሮችም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕከት ማስተላለፋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አስታውቋል።

ኢትዮጵያ አዲስ ዓመቷን ተቀብላለች

ኢትዮጵያ አዲስ ዓመቷን ተቀብላለች

የራሷን የቀን አቆጣጠር የምትከተለው ኢትዮጵያ አዲስ ዓመቷን ተቀብላለች።

ያለፉት የጳጉሜን ቀናት በተለያዩ ሁነቶች ያለፉ ሲሆን፥ አዲስ ዓመትን መግባት ምክንያት በማድረግ በሚሌኒየም አዳራሽ ታላቅ የሙዚቃ ድግስ ተሰናድቶም ነበር።

በዚህ ዝግጅት ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ጨምሮ የክልል ርእሳነ መስተዳድራን እና በቅርቡ ወደ ሀገራቸው የተመለሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ተገኝተዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዝግጅቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክትም፥ ለብዙ ዓመታት ከእናት አገራቸው ተለይተው ለቆዩና በቅርቡ ወደ አገራቸው ለመጡት ፖለቲከኞች፣ አክቲቪስቶች እና ለሌሎች የዳያስፖራ ማህበረሰቦች በሙሉ እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል።

አክለውም አዲሱ ዓመት የጋራ ግባችን እጅግ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ህዝባችን ለጋራ ብልጽግና ተግቶ እንዲሰራ በማስቻል የተረጋጋና ለልማት የተሰለፈ የአፍሪካ ቀንድን ዕውን ማድረግ ይሆናል ብለዋል።

አዲስ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ በመላው ሀገሪቱ የተለያዩ ሁነቶች የተሰናዱ ሲሆን፥ በተለይም በአዲስ አበባ የተለያዩ የዋዜማ የሙዚቃ ድግሶች ተሰናድተዋል።

በተለይም በአዲስ አበባ የአዲስ ዓመት አቀባበሉን የርችት ስነ ስርዓት ደማቅ አድርጎታል።

ኢትዮጵያን ለመገንባት ከአንድነት ተኳርፈን፤ ከነጻነት ተፋተን ሳይሆን በፍቅር በመደመር ወደፊት መትመም አለብን - ጠ/ር ዶ/ር አብይ አህመድ



ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ

(ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአዲስ አመት ዋዜማ ልዩ የበዓል ዝግጅት ላይ ባስተላለፉት መልክት የጋራ ቤታችን የሆነችውን ኢትዮጵያን ለመገንባት ከአንድነት ተኳርፈን፣ ከነጻነት ተፋተን ሳይሆን በፍቅር በመደመር ወደፊት መትመም አለብን ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በዚሁ ንግግራቸውም የኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት በማመን በአዲሱ አመት ፕሮግራም ላይ ለመታደም ከተለያዩ ሀገራት ለተገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ አክቲቪስቶችና የሰባዊ መብት ተመጋቾች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የዘንድሮው አዲስ ዓመት ከ20 ዓመታት በኋላ ኢትዮጵያና ኤርትራ አንደገና በጋራ የሚከብሩት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሁለቱ ሀገራት ህዝቦችና ለሌሎች ወዳጅ ሀገራት ህዝቦች የእንኳን አደረሳችሁ መልክት አስተላልፈዋል።

ባለፉት ጊዚያት ሀገሪቱ በአስከፊ ሁኔታዎች ስር የነበረች መሆኑን ያስታወሱት ጠላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሀገሪቱ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ተጋርጠውባት የነበረ መሆኑንና ወጣቶቹም በአመጽና በሞት ጥላ ሰር የነበሩ መሆኑን ተናግረዋል።

ያለፈው ዓመት ሰባዊ ቀውስ የተባባሰበትና በተለየዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከፍተኛ ዜጎች ተፍናቅለውበት የነበረ መሆኑን አመላክተዋል።

ይሁን እንጂ በአሮጌው ዓመት መጨረሻዎች ወራት በተለይም ያለፉት አምስት ወራት የታሰሩ የተፈቱበት የተለያዩ የተገናኙበትና በሃገሪቱ አንድነት ዙሪያ መነቃቃት የታየባቸው ናቸው ብለዋል።

በዚህም ፍቅር አንድነትና መደመር በመላ ሀገሪቱ በማስተጋበት የተስፋ፣ ብርሃንና ሰላም የፈነጠቀና ሲሆን፥ ኢትዮጵያዊን ተስፋችን አንደ አደይ አበባ በማፍካት ላይ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

አዲስ አመት እያከበርን በትናንት የምንጨቃጨቅ ከሆነ ግን ዘመኑ እንጂ እኛ አልተቀየርንም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፊታችንን ወደ ትናንት በመዞር ወደፊት መጓዝ አንችልም ሲሉም አክለው ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የጋራችን ቤት እንድትሆን አንዳችን ለአንዳችን በመደጋገፍ መስራታ ይጠበቅብናልም ብለዋል።

በአዲሱ አመት በኢትየጵያዊነቱ የሚገፋ ዜጋ የማይኖር መሆኑን ተስፋቸውን የገለጹት ዶክተር አብይ በአዲሱ ዓመት ምርጫዎችን ዴሞክራሲና እወነተኛ ለማድረግ እና ያልደረስንባቸው ከፍታዎችን ለመድረስ እንሰራለን ብለዋል።

በዚህም ከተስፋ ያለፈ ተጨባጭ ለውጥ እንዲኖርም የጋራ መግባባት ላይ መድረስና ከራሳችን መታረቅ አለብን ሲሉ አስረድተዋል።

በዓዲሱ የ2011 ዓመት የርቅና የሰላም ጊዜ እንደሚኖር ያመላከቱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አዲሱ ዓመት ከስርዓተ አልበኝነት ወደ ህጋዊ አሰራር የምንኘጋገረበት፣ የመንግስት ሹመኖች በስልጣን አገልጋይ የሚሆኑበት እንዲሁም ዜጎቹ በትጋታቸውና በላባቸው ተጠቃሚ የሚሆኑበት እንደሚሆን ተስፋቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም የፖለቲካ ፓርቲዎች ጎራ ላይተው አንዳቸው ሌላቸውን የማይዘላለፉበት፣ አክቲቪስቶች የነጻነት፣ ታጋዮች ሀገራዊ ብሎም አህጉራዊ አስተሳሰብ የሚያንጸባረቁበት እንዲሆንም ነው የገለጹት።

ከዚህም ሌላ ጋዜጠኞች 4ኛ የመንግስት አካል መሆናቸውን የሚያረጋግጡበትና አውነታወችን ፈልቅቀው በማውጣት ለህግ የበላይነት የሚታገሉበት እንደሚሆንም አስረድተዋል።

''በሐረሯ ሕጻን ጫልቱ ሞት የተጠረጠረው ግለሰብ እስካሁን ክስ አልተመሠረተበትም'' - ቢቢሲ

''በሐረሯ ሕጻን ጫልቱ ሞት የተጠረጠረው ግለሰብ እስካሁን ክስ አልተመሠረተበትም'' - ቢቢሲ

በ14 ዓመቷ ጫልቱ አብዲ ላይ አሰቃቂ ጥቃት አድርሷል የተባለው ግለሰብ እስከዛሬ ክስ እንዳልተመሠረተበት ጉዳዩን የሚከታተሉት ጠበቃ ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩት በኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር ከፍተኛ የሕግ ባለሙያ የሆኑት ወይዘሮ ኤልሳቤጥ ከበደ ግልጽ ባልሆኑ ምክንያቶች ግለሰቡ ላይ ክስ ሳይመሠረት አራት ወራት መውሰዱንም ጠቁመዋል።

ፖሊስ ማስረጃ ሰብስቦ ለአቃቢ ሕግ ሲያስተላልፍ መደበኛ ፍርድ ቤት ፋይል እንደሚከፈት የሚናገሩት ጠበቃዋ እስካሁን ግን በተጠርጣሪው ላይ መደበኛ ፍርድ ቤት ክስ አልተመሠረተም።

ክሱ ለምን እንደዘገየ የተጠየቁት ጠበቃዋ ጉዳዩን የያዙት የክልሉ ፖሊስ መርማሪዎች የሐኪም ማስረጃ ሐረር ድረስ ወስደው ለማስተርጎም በሚል አላስፈላጊ ጊዜ እንደወሰዱ አስረድተዋል።

ክስ ለመመሥረት በሚጠበቅበት ጊዜም ሐረር ድረስ ይዘውት የሄዱትን የሐኪም ማስረጃ «የትርጉም ስህተት አለው» በሚል በድጋሚ አዲስ አበባ ተመልሰው «ተጨማሪ ማስረጃ ፈልገን ነው የመጣነው» በሚል ክስ እንዳዘገዩም ነግረውናል።

የሆስፒታል ማስረጃ በእንግሊዝኛ እንደሚጻፍ፣ የፍርድ ቤት የሥራ ቋንቋ ደግሞ አማርኛ በመሆኑ ማስረጃው መተርጎሙ አስፈላጊ እንደሆነ ካብራሩ በኋላ፣ የሐኪም ማስረጃን ለማስተርጎም አዲስ አበባ በብዙ መልኩ ከክልል የተሻለ እንደሆነ የታወቀ ቢኾንም፤ ፖሊስ ማስረጃውን ክልል ድረስ ይዞ መሄድ ለምን እንዳስፈለገው ለጠበቃ ኤልሳቤጥ ግልጽ አልሆነላቸውም።

የሐኪም ማስረጃን ከወሰዱ በኋላ አራት ሆነው በድጋሚ ተመልሰው መምጣታቸውንና ማስረጃውን ይዘው የካቲት 12 ሆስፒታል መሄዳቸውን ጠቅሰዋል። ለአራት ወራት ክስ ላለመሥረት ምክንያታቸውም ይኸው ነው ብለዋል።

በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓቱ መሠረት አንድ ፖሊስ ከ21 ቀን በላይ ጊዜ ቀጠሮ ማቆየት አይችልም የሚሉት ጠበቃዋ፤ ፖሊስ ማስረጃ አልተሟላልኝም ካለ ሦስት ጊዜ ሰባት ሰባት ቀናት ማራዘም እንደሚችል ጠቅሰዋል። ነገር ግን እስከ አራት ወራት ክስ ሳይመሰረት ማለፉ እንዳስገረማቸው አብራርተዋል።

''ባለፉት ወራት ሟች ቃል ትሰጣለች፥ ፖሊስ ተመላልሶ ይመጣል። ለምን ክስ መመሥር እንዳልፈለጉ ግልጸ አይደለም።''

የሆስፒታሉ ማስረጃ ምን እንደሚያሳይ የተጠየቁት ጠበቃዋ የሞቷ መንስኤ ምን እንደሆነ ያስረዳል ብለዋል።

"18 በመቶ ሰውነቷ በቃጠሎ ተጎድቷል። ይህም ከጡቷ ሥር እስከ ጉልበቷ ይደርሳል። ቃጠሎው ወደ ጀርበዋም ዘልቋል።" ይላሉ።

ጠበቃ ኤልሳቤት ጨምረው እንደተናገሩት መጀመሪያ ተጠርጣሪና ተባባሪዎቹ ልጅቷን እንዳስፈራሯትና በኋላ ላይ ግን በፖሊስ ስትጠበቅበት ከነበረ ክፍል ውስጥ ላገኘቻቸው ሰዎች የደረሰባትን መናገሯን ጠቅሰው፤ ለኔም መደፈሯን ነግራኛለች ብለዋል።

ሟችን በሆስፒታል ሳለች ብልቷ አካባቢ ከጥቅም ውጭ ሆና እንደነበረና በመደፈር ስንጥቅ ስለደረሰባት ምናልባትም ያንን ለመሸፈን ሲባል ቃጠሎ እንደደረሰባት የሚገምቱም አልጠፉም። ጠበቃዋም ተመሳሳይ ግምት አላቸው።

''ምንም ሳትሆን የተቃጠለች ቢሆን ኖሮ እንዳለ ሁሉም ነጭ ይሆን ነበር። ከማህጸኗ እስከ ፊንጢጣዋ ድረስ ስንጥቅ አለው። እዛጋ ደም አለው። ለነርሱ [ለሐኪሞች] ትንገራቸው አትንገራቸው፥ ወይም ደግሞ በምርመራ ሂደት ይድረሱበት አይድረሱበት አላውቅኩም። ግን ለኔ የሆነችውን ነግራኛለች።'' ብለዋል።

ሟች ላይ ጥቃት ከደረሰ በኋላ ወላጆቿ አቅም ስላልነበራቸው የካቲት 12 ሆስፒታል የሚያሳክምላችው እንዳልነበረ ያወሱት ጠበቃዋ፤ በኋላ ላይ በፌስቡክ በተሰበሰበ እርዳታ 32ሺ ብር መገኘቱንና ልጅቱ በሱ መታከም መጀመሯን አስታውሰዋል።

የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር ዳይሬክተር ወ/ሮ ሜሮን አራጋው ጫልቱ ጥቃቱ ከተፈፀመባት በኋላ ያለምንም እርዳታ በተደፈረችበት ቤት ውስጥ ለ15 ቀናት እንድትቆይ መደረጉን ለቢቢሲ ገልፀዋል። የታዳጊዋ ቃጠሎም ሦስተኛ ደረጃ ማለትም አጥንት ዘልቆ የሚገባ እንደነበርም አመልክተዋል።

ቢቢሲ የሟችን እናትና አባት ለማግኘት ሙከራ ያደረገ ቢሆንም ስልክ ስለሌላቸው ማግኘት አዳጋች ሆኗል።
"በክልሉ ልዩ ኃይል ጥበቃ ይደረግላት ነበር"

የ14 ዓመት ታዳጊዋ ጫልቱ አብዲ በአሰሪዋ ተገዳ ከተደፈረች በኋላ ምንነቱ ያልታወቀ ፈሳሽ ተደፍቶባታል ተብሏል። በዚህም ታዳጊዋ ከጉልበትዋ እስከ እምብርቷ ድረስ ከፍተኛ የመቃጠል ጉዳት እንደደረሰባት ተገልጿል።

ከምሥራቅ ሐረርጌ በደኖ ከሚባል ቦታ ወደ ሐረር የመጣችው ታዳጊ፤ በተጠርጣሪው ቤት ውስጥ በቤት ሠራተኝነት ተቀጥራ ነበር የምትሰራው።

ጉዳዩን ሲከታተሉ የነበሩት ከፍተኛ የሕግ ባለሙያ ኤልሳቤጥ እንደሚሉት ታዳጊዋ ከመደፈሯ በተጨማሪ በሰውነቷ ላይ የተደፋባት ፈሳሽ ያደረሰባት ጉዳት እያለ ምንም ዓይነት ሕክምና ሳታገኝ በቤት ውስጥ እንድትቆይ ተደርጋለች። ''ሕመሙ እየባሰባት ሲመጣና ሕይወቷ አስጊ ደረጃ ላይ ሲደርስ ወደ ሐረር ምሥራቅ አርበኞች ሆስፒታል በድብቅ ተወስዳለች።''

በሆስፒታሉ ውስጥም ማንም ሰው እንዳያያት ባዶ ክፍል ውስጥ እንድትተኛና ሌሎች ሰዎች ወደ ክፍሉ እንዳይገቡ በክልሉ ልዩ ኃይል ጥበቃ ይደረግባት እንደነበረ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ''የሚከታተላት ነርስም ቢሆን ከውጪ ነው የተቀጠረው'' በማለት የጉዳዩን ውስብስብነት ያመለክታሉ።

ሁኔታው ጥርጣሬ የጫረባቸው የሆስፒታሉ ሠራተኞችና ሌሎች አስታማሚዎች ወደ ክፍሉ ለመግባት ጥረት ሲያደርጉም በወታደሮቹ ይከለከሉና ይባረሩ እንደነበረ ነግረውናል ይላሉ ጠበቃ ኤልሳቤጥ። በመጨረሻ ተሳክቶላቸው መግባት የቻሉ ሰዎች አስር ታካሚዎችን በሚያስተናግድ ክፍል ውስጥ ለምን ብቻዋን እንደተኛች ሲጠይቋት፤ የደረሰባትን ነገር እንዳስረዳች ጠበቃዋ ያመለክታሉ።

ጥቃቱን ያደረሰባት ግለሰብ ባለትዳር ሲሆን፤ የተጠርጣሪው ባለቤትም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር ውላ ከአንድ ቀን በኋላ መፈታቷን ወይዘሮ ኤልሳቤጥ ነግረውናል።
"ሐረር ካልተቀበረች ብለው መቃብር ቆፍረው ነበር"

ለደኅንነታቸው ሲሉ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉና የጫልቱን ጉዳይ በቅርብ የሚከታተሉ አንድ ግለሰብ ጉዳዩን ለመሸፋፈን የተጠርጣሪው ቤተ ዘመድና በሐረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አስተዳደር ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጭምር እጃቸውን ያስገቡ እንደነበር ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ሕክምናውን አስመልክቶ በቴሌቨዥን እሷን የተመለከቱ መርሐግብሮች እንዳይተላለፉ ጫና መደረጉን፣ ከዚያም ባሻገር ቃሏን እንድትቀይር የሚያደርጉ ተጽእኖዎችም ነበሩ ተብሏል።

ወይዘሮ ሜሮን አራጋው ከእናቷ አንደበት ሰማሁ ብለው ለቢቢሲ እንደተናገሩት ደግሞ ጫልቱን ሐረር ሕክምና ላይ ሳለች መሣሪያ የያዙ ፖሊሶች ናቸው ሲጠብቋት የነበረው። "ይህም ጉዳዩ ተድበስብሶ እንዲቀር ሙከራ ይደረግ እንደነበር ያሳያል" ብለዋል።

እነዚህን ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ በማስገባት የፍርድ ሒደቱ ምን ያህል ነጻ ሊሆን ይችላል በሚል የተጠየቁት ወይዘሮ ሜሮን ፍርድ ሂደቱ ሐረር ክልል ላይ ቢታይ መጨረሻ ላይ የሚሰጠው ፍትህ ላይ ተጽእኖ እንደሚኖረው ለፌዴራል ጠቅላይ አቃቢ ሕግ አቤት ማለታቸውን ገልጸው "የፌዴራሉ ጠቅላይ አቃቢ ሕግም ምላሽ ሰጥቶናል።" ብለዋል።

በገንዘብ የማባበል ሙከራን ጨምሮ የተጠርጣሪ ቤተሰቦች የተለያየ የማዋከብ ሥራ ሲሠሩ ነበር ያሉት እኚህ ግለሰብ፤ ቀብሯ በተወለደችበት ቀዬ እንዳይፈጸም ይልቁንም ሐረር ከተማ ካልተቀበረች ብለው መቃብር ቆፍረውም እንደነበርም ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉት ግለሰብ ገልፀዋል።

የሶማሌ ክልል የቀድሞው ሰንደቅ አላማ ዳግም ጥቅም ላይ እንዲውል ተወሰነ - ቢቢሲ

የሶማሌ ክልል

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል በጠራው ልዩ ስብሰባዉ የቀድሞ የክልሉ ሰንደቅ አላማ ተመልሶ የክልሉ መለያ ሆኖ እንዲያገለግል ወሰነ።

ከዓመታት በፊት ለውጥ ተደርጎበት የነበረው በከፊል የሶማሊያ የሰንደቅ ዓላማ ሰማያዊ ቀለምና ነጭ ኮከብ ያለው ሰንደቅ ተመልሶ እንዲያገልግል ተወስኗል። ቀደም ሲል የነበረው ሰንደቅ አላማ በከፊል ቢጫ ቀለምና የግመል ምስል ይዞ ቆይቶ ነበር።

በቅርቡ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር የሆኑት አቶ ሙስጠፋ ዑመር በፌስቡክ ገጻቸው በክልሉ ሰንደቅ አላማ ላይ ለውጥ መደረጉን በተመለከተ በማህበራዊ ገፃቸው ላይ "በሶማሌነታችንና በኢትዮጵያዊነታችን መሀከል ተቃርኖ የለም" ሲሉ አስፍረዋል።

የቀድሞው ሰንደቅ አላማ ተመልሶ ሥራ ላይ መዋል መጀመሩን በተመለከተም "የሶማሌ ክልል ህዝቦች ነን፤ ከፊትም ከኋላም ቅጥያ የለም፤ የቀደመው ሰንደቅ አላማ ተመልሷል" በማለት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በገፃቸው ላይ ገልፀዋል።

የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደድር አቶ አብዲ ሙሀመድ ዑመር ከስልጣን ከተነሱ በኋላ የተተኩት አቶ ሙስጠፋ ዑመር፤ "የሶማሌነት መገለጫችንን በኩራት ስንጠብቅ ብሔራዊ ግዴታችንንም ባለመዘንጋት ነው" ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ምክር ቤት በዛሬው ልዩ ስብሰባው አዲስ አፈ-ጉባኤ ለምክር ቤቱ የሰየመ ሲሆን ለዳኞችም ሹመት ሰጥቷል።