በወያኔ የአፓርታይድ አገዛዝ ተቃውሞ ቢቀርብበትም በጋና መንግሥት ብርታትና ግፊት የሌሎችን የአፍሪካ አገሮች ይሁንታ በማግኘቱ በአፍሪካ ኅብረት ቅጥር ግቢ ግንባታው የተጀመረው የእውነተኛው አፍሪካ አባት የግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሐውልት በመጪው ጥር ወር እንደሚመረቅ ኅብረቱ አስታውቋል።
መለስ ዜናዊ ክዋሜ ንክሩማህን የአፍሪካ አባት ያደረገው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ያዋረደ መስሎት ነበር። ሆኖም ግን እውነት ይዘገያል እንጂ ተደብቆ አይቀርምና በእውነተኛ የአፍሪካ ልጆች ተጋድሎ የእውነተኛው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አባት መታሰቢያ ሐውልት ለምርቃት ሊበቃ ነው።
ከታት የታተመው ድምጽ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የመጀመሪያው የክብር ፕሬዝደንት የሆኑት ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እንዲመሰረት ግንቦት 14 ቀን 1955 ዓ.ም. ያሰሙት ታሪካዊ ንግግር ነው።
No comments: